ለጀማሪ የቢዝነስ መስራቾች ስልጠና

ትምህርት 1. ግብ መወሰን እና ራዕይ ማስማማት

 

ፍቺ/ትርጉም:

ግብ መወሰን ለስራ ፈጣሪነት ጉዞዎ ትኩረት መስጠትዎን እና አቅጣጫ ማስያዝዎን በማረጋገጥ ከረጅም ጊዜ ዓላማዎችዎ ጋር የሚስማሙ ግልጽና የተግባር ዓላማዎችን የመወሰን ሂደት ነው፡፡

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • የዕለት ከዕለት ተግባሮችን ከረጅም ጊዜ ግቦች ጋር የማስማማት አስፈላጊነትን መረዳት፡፡
  • እንዴት የSMART (ዓላማ ተኮር፣ ሊለኩ የሚችሉ፣ ሊሳኩ የሚችሉ፣ ተገቢ፣ በጊዜ የተገደቡ) ግቦች ማዘጋጀት እንደሚቻል መማር፡፡
  • አካሄድን ለመከታተል እና በተነሳሽነት ለመቀጠል ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት፡፡

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • የግልና የንግድ ስራ ራዕይዎን መግለጽ፡፡
  • ረጅም ግቦችን ወደ የአጭር ጊዜ መለኪያዎች መከፋፈል፡፡
  • ለማደራጀት እንደ የግብ መወሰኛ ቴምፕሌቶች ወይም የራዕይ ሰሌዳዎች የመሳሰሉ መሳሪያዎችን መጠቀም፡፡
  • በግብረመልስና ውጤቶች ላይ ተመስርቶ ግቦችን መገምገምና ማስተካከል፡፡

 

ትምህርት 2. የጊዜ አጠቃቀምና ቅደም ተከተል መስጠት

ፍቺ/ትርጉም:

የጊዜ አጠቃቀም ከፍተኛ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ስራዎች ጊዜን ውጤታማ በሆነ መልኩ ማደራጀትና መመደብን የሚይዝ ሲሆን ቅደም ተከተል መስጠት ሀብቶች ከፍተኛ ውጤት ላላቸው ስራዎች መመደባቸውን ያረጋግጣል፡፡  

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • ተወዳዳሪ ፍላጎቶችን ለማስተዳደር እንደ የጊዜ ምደባና ቅደም ተከተል መስጫ ዘዴዎች የመሳሰሉ ስልቶችን ማወቅ፡፡
  • በአስቸኳይ እና አስፈላጊ ስራዎች መካከል ያለውን ልዩነት ማወቅ፡፡
  • መረበሾችን ለመቀነስና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ስትራቴጂዎችን መለየት፡፡

ዋና ዋና የትምህርት ነጥቦች:

  • ከፍተኛ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ስራዎች ልዩ ጊዜ መመደብ፡፡
  • መሰላቸትን ለማስቀረትና ስራ-ህይወትን ለማመጣጠን ገደቦች ማስቀመጥ፡፡
  • ውጤታማ አለመሆኖችን ለመለየት ለስራዎች የተሰጠውን ጊዜ መከታተል፡፡

 

ትምህርት 3. ዝግጁነትና የአእምሮ ጥንካሬን ማጎልበት

ፍቺ/ትርጉም:

ዝግጁነት እንቅፋቶችን የመላመድና የመወጣት ችሎታ ሲሆን የአእምሮ ጥንካሬ ስራ ፈጣሪዎችን በጫና ውስጥም ትኩረት ሰጥተውና አዎንታዊ አመለካከት ይዘው እንዲቀጥሉ ያስችላቸዋል፡፡

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • ጫናን፣ ተቀባይነት ማጣትን እና ውድቀትን ማለፊያ ስትራቴጂዎችን ማጎልበት፡፡
  • የስነ ልቡና ደህንነትን ለማስጠበቅ የአስተዋይነት ስልቶችን መማር፡፡
  • እንደ የራስ ገለጻና የምስጋና አሰራሮች ያሉ ዝግጁነትን ማጠናከሪያ ልማዶችን ማጎልበት፡፡

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • ውድቀቶችን እንደ የመማሪያ ዕድሎች አድርጎ መውሰድ፡፡
  • ችግሮችን ለማጋራትና ምክር ለመጠየቅ ጠንካራ የድጋፍ ስርዓት ማዘጋጀት፡፡
  • እንቅፋቶችን ለማለፍ እድገት ተኮር አስተሳሰብ መያዝ፡፡

 

ትምህርት 4. የዕድገት አስተሳሰብ ማጎልበት

ፍቺ/ትርጉም:

የዕድገት አስተሳሰብ ችሎታዎችና እውቀት በጥረት፣ ትምህርትና ጽናት አማካኝነት እያደጉ እንደሚሄዱ ማመን ነው፡፡

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • ተግዳሮቶችን መላመድና እንደ የእድገት እድሎች አድርጎ መውሰድ፡፡
  • ግብረ መልስ ስለመጠየቅና ገንቢ እርምጃ ስለመውሰድ መማር፡፡
  • የመሞከርና የመደጋገም ጉጉትና ፍላጎትን ማስረጽ፡፡

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • በመጻህፍት፣ ኮርሶች ወይም ምክሮች አማካኝነት መማር ላይ ማተኮር፡፡
  • በራስ መተማመን እና ተነሳሽነትን ለማጎልበት በትናንሽ ድሎች መደሰት፡፡
  • የተገኙ ትምህርቶችን ለመለየት የቀደመ ጊዜ ተሞክሮዎችን መግለጽ፡፡
  • ለችግር አፈታት ሙከራና ፈጠራን ማበረታታት፡፡

 

ትምህርት 5. እርግጠኛ ባለመሆን ውስጥ ውሳኔ ማሳለፍ

ፍቺ/ትርጉም:

እርግጠኛ ባለመሆን ውስጥ ውሳኔ ማሳለፍ ያልተሟላ መረጃ ወይም የማይገመቱ ውጤቶች በሚያጋጥሙበት ጊዜ ውስጥም በመረጃ የተደገፉ ምርጫዎችን መምረጥን ይይዛል፡፡

የትምህርቱ አላማዎች:

  • አማራጮችን ለመገምገም እንደ የSWOT ትንተና ወይም የወጪ-ጥቅም ትንተና ያሉ ማዕቀፎችን መማር፡፡
  • ስጋቶችን እና ሽልማቶችን ውጤታማ በሆነ መልኩ የመመዘን ችሎታን ማዳበር፡፡
  • ያለው ውሱን ዳታ ቢሆንም ወቅቱን የጠበቁ ውሳኔዎች ለማሳለፍ በራስ መተማመንን ማጎልበት፡፡

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • በተቻለ መጠን ከውሳኔ በፊት የሚቻለውን ያክል ተገቢ ዳታ መሰብሰብ፡፡
  • የተለያዩ ሀሳቦች ለማግኘት አማካሪዎች ወይም እኩዮችን ማነጋገር፡፡
  • አማራጮችና ውጤቶችን ለማየት የውሳኔ መስጫ መሳሪያዎች መጠቀም፡፡
  • የወደፊት ማስተካከያን ለማሻሻል የቀደመ ጊዜ ውሳኔዎችን መግለጽ፡፡

 

ትምህርት 6. የውጤታማ ግንኙነት ክህሎቶች

ፍቺ/ትርጉም:

ውጤታማ ግንኙነት ሀሳቦችን በግልጽ የማስተላለፍ፣ በንቃት የማዳመጥ እና ከሌሎች ጋር ትርጉም ያላቸው ግንኙነቶች የመፍጠር ችሎታ ነው፡፡

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • ራዕይዎን ሳቢ በሆነ መልኩ ለመግለጽ የታሪክ መንገሪያ ስልቶችን ማወቅ፡፡
  • የሌሎችን ሀሳቦች ለመረዳት በንቃት የማዳመጥ ክህሎቶችን መማር፡፡
  • ሀሳቦችን ለማስተጋባት ወይም አለመግባባቶችን ለመፍታት የማሳመኛ ግንኙነት ክህሎቶችን ማጎልበት፡፡

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • መልዕክትዎን ከተለያዩ አድማጮች ጋር ያስማሙ፡፡
  • በቃልና የጽሁፍ ግንኙነት ላይ ግልጽትና አጭርነትን ይለማመዱ፡፡
  • የመልዕክቱን መድረስ ለማሻሻል የአካል ቋንቋና የድምጽ ቃና መጠቀም፡፡
  • የግንኙነት ዘይቤዎን ለማሻሻል ግብረ መልስ መጠየቅ፡፡

 

ትምህርት 7. ትስስርና ግንኙነትን ማጎልበት

ፍቺ/ትርጉም:

ትስስር እድሎችን ለማስፋት፣ ድጋፍ ለማግኘት እና ትብብርን ለማጠናከር ሙያዊ ግንኙነቶችን መፍጠርና ማጎልበትን ይይዛል፡፡

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • እጩ አማካሪዎችነብ፣ ባለሀብቶችን እና አጋሮችን እንዴት እንደሚቀርቡና እንደሚያሳትፉ መማር፡፡
  • በመተማመን እና የጋራ ጥቅም ላይ ተመስርቶ የተረጋገጡ ግንኙነቶችን መፍጠር፡፡
  • እንደ ሊንክድ ኢን ወይም የኢንዱስትሪ ዝግጅቶች ያሉ የትስስር ፕላትፎርሞችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ማጠናከር፡፡

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • ተመሳሳይ አመለካከት ካላቸው ግለሰቦች ጋር ለመገናኘት በአውደ ጥናቶች፣ ኮንፍረንሶች ወይም ስብሰባዎች ላይ መሳተፍ፡፡
  • ግንኙነቶችን ለማስቀጠል በመደበኝነት ክትትል ማድረግ፡፡
  • እርዳታ ከመጠየቅ በፊት ለሌሎች ጥቅም መስጠት፡፡
  • ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ለማግኘት የስራ ፈጣሪ ቡድኖች ወይም የኦንላይን ማህበረሰቦችን መቀላቀል፡፡

 

ትምህርት 8. ውክልናና የቡድን አመራርነት

ፍቺ/ትርጉም:

ውክልና ስራዎችን ለቡድን አባላት የመመደብ ሂደት ሲሆን የቡድን አመራር የጋራ አላማዎችን ለማሳካት ቡድኖችን መምራትና አቅማቸውን ማጎልበትን ይይዛል፡፡

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • በቡድን ጥንካሬዎች ላይ ተመስርቶ ሊመደቡ የሚችሉ ስራዎችን መለየትን መማር፡፡
  • ቡድንዎን ለማነሳሳትና ለማበረታታት የአመራርነት ክህሎቶችን ማዳበር፡፡
  • በቡድን ውስጥ ተጠያቂነትና መተማመንን ማጎልበት፡፡

 

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • ለእያንዳንዱ የቡድን አባል የስራ ድርሻዎችና ኃላፊነቶችን በግልጽ መግለጽ፡፡
  • ሞራልን ለማሳደግ ገንቢ ግብረ መልስና ዕውቅና መስጠት፡፡
  • ቡድንዎን ያለ ጥቃቅን ቁጥጥር ስራዎችን እንደሚፈጽም ማመን፡፡
  • ሁሉም ሰው ዋጋ እንደተሰጠው እንዲሰማው የሚያደርግ የትብብር ምህዳር መፍጠር፡፡

 

ትምህርት 9. የግጭትና ችግር አፈታት

ፍቺ/ትርጉም:

የግጭት አፈታት አለመግባባቶችን ገንቢ በሆነ መልኩ መፍታትን የሚይዝ ሲሆን የችግር አፈታት ለችግሮች ውጤታማ መፍትሄ በመፈለግ ላይ ማተኮርን ይይዛል፡፡

የትምህርቱ ዓላማዎች:

  • ግጭቶችን በሰላማዊ ሁኔታና በትብብር የመፍቻ ስልቶችን መማር፡፡
  • ውስብስብ ችግሮችን ለመፍታት የፈጠራ የችግር አፈታት ክህሎቶችን ማዳበር፡፡
  • በቡድን አባላት ወይም ባለድርሻ አካላት መካከል አለመግባባቶችን የማሸማገል ችሎታን ማጎልበት፡፡

 

ዋና ዋና የሚዳሰሱ ነጥቦች:

  • አለመግባባት ውስጥ የገቡ ሁሉንም ወገኖች በንቃት ማዳመጥ፡፡
  • ከምልክቶች ይልቅ ስረ መንስኤዎችን መለየት ላይ ማተኮር፡፡
  • የተለያዩ መፍትሄዎችን ማሰላሰልና አዋጭነታቸውን መገምገም፡፡
  • መፍትሄዎችን በግልጽነት መተግበርና ውጤቶቹን መቆጣጠር፡፡
Scroll to Top