Course Content
ምእራፍ 3፡ ደንበኛን ያማከለ ትኩረት
ፍቺ/ትርጉም ደንበኛን ያማከለ ትኩረት ትኩረት የሚያደርጉባቸውን ደንበኞች በጥልቀት የመገንዘብ እና ልዩ ፍላጎቶቻቸውን፣ ምርጫዎቻቸውን የሚያሟላና ችግሮቻቸውን የሚፈቱ መፍትሄዎችን የማዘጋጀት አሰራር ነው፡፡ በኢትዮጵያ ንጹህ የማብሰያ ዘርፍ አውድ ይህ ደንበኞችን በስነ ህዝብ (ምሳ፡ ዕድሜ፣ ጾታ፣ ገቢ)፣ ባህሪ (ምሳ፡ የምግብ ማብሰያ ልማዶች፣ የማገዶ ምርጫዎች) እና ልዩ ፍላጎቶች (ምሳ፡ ለገጠር አባወራዎች የዋጋ ተመጣጣኝነት፣ ለከተማ ነዋሪዎች አመቺነት) ላይ ተመስርቶ ደንበኞችን መክፈልን ይይዛል፡፡ ደንበኛን ያማከለ አቀራረብ በመከተል ስራ ፈጣሪዎች መፍትሄዎቻቸው አግባብነት ያላቸው መሆናቸውን፣ ተደራሽ መሆናቸውን እና ውጤት የሚያመጡ መሆናቸውን ያረጋግጣሉ፡፡
0/12
በተግባር የመጀመሪያ የንግድ ሥራ ሞዴል ረቂቅዎን ማዘጋጀት – በአማርኛ

የትምህርቱ ዓላማ

በዚህ ትምህርት መጨረሻ ላይ ተሳታፊዎች በንፁህ ማብሰያ ዘርፍ ላይ የንግድ ሥራ ሃሳቦቻቸውን ስልታዊ በሆነ መንገድ ለመቅረፅ ዘጠኙን የመነሻ ነጥቦች በመጠቀም የመጀመሪያውን የመጀመሪያውን የንግድ ሥራ ሞዴል ረቂቃቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ፡፡

 

ተሳታፊዎች እንዴት ዋና ዋና የደንበኛ ችግሮችን እንደሚለዩ፣ እንዴት ትኩረት የሚደረግባቸው የደንበኛ ምድቦችን እንደሚገልጹ፣ እንዴት ልዩ የዕሴት እቅድን እንደሚገልጹ፣ እንዴት የገቢ ማግኛ መስመሮችን እንደሚዘረዝሩ፣ እና እንዴት የወጪ መዋቅሮችን እንደሚገመግሙ ያውቃሉ፡፡

ይህ የተግባር ትምህርት አዳዲስ የስራ ፈጣሪዎችን እሳቤዎቻቸውን የሚያረጋግጡበት፣ በተጨባጭ የገበያ ፍላጎቶች ላይ የሚያተኩሩበት እና ለውጤታማ የሀብት ምደባ ቅድሚያ የሚሰጡበት ተግባራዊ ማዕቀፍን በማሳወቅ የንግድ ሥራ ሀሳቦቻቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ማህበረሰቦችን ተጨባጭ ተግዳሮቶች/ ችግሮች በመፍታት ላይ የተመሰረቱ መሆናቸውን እንዲያረጋግጡ ያስችላቸዋል፡፡

 

Scroll to Top